Fana: At a Speed of Life!

አቶ ደመቀ መኮንን በተባበሩት አረብ ኤመሬትስ የስራ ጉብኝት አደረጉ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 15 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን በተባበሩት አረብ ኤመሬትስ የስራ ጉብኝት አካሂደዋል።

ለሁለት ቀናት በነበራቸው ቆይታ ከተባበሩት አረብ ኤመሬትስ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች ጋር ተገናኝተው መክረዋል።

የሁለቱ ሃገራትን ግንኙነት የበለጠ ለማጠናከር እንዲሁም በቀጣይ በተለያዩ ዘርፎች ሃገራቱ በሚኖራቸው ትብብር ዙሪያ ተወያይተዋል።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ በተባበሩት አረብ ኤመሬትስ የነበራቸውን የስራ ተልዕኮ በማጠናቀቅ ወደ ሞስኮ አቅንተዋል፡፡

አቶ ደመቀ ከሩሲያ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ ጋር ተገናኝተው እንደሚወያዩ ከማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

በሞስኮ በሚኖራቸው የስራ ቆይታ ኢትዮጵያ ያለችበትን ወቅታዊ ሁኔታ ለማስረዳት እና በሃገራቱ መካከል ያለውን ታሪካዊ ግንኙነት በተለያዩ መስኮች የበለጠ ለማጠናከር ያለመ መሆኑን ለመረዳት ተችሏል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.