የምዕራብ ጎጃም ዞን ነዋሪዎች ከ290 በላይ ሰንጋና ፍየል ለሀገር መከላከያ ሰራዊትና ለአማራ ልዩ ሀይል ድጋፍ አደረጉ
አዲስ አበባ ፣ ህዳር 3 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የምዕራብ ጎጃም ዞን ነዋሪዎች ከ290 በላይ ሰንጋና ፍየል ለሀገር መከላከያ ሰራዊትና ለአማራ ልዩ ሀይል ድጋፍ አደረጉ፡፡
የምዕራብ ጎጃም ዞን የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ ሀላፊ አቶ አንማው ዳኛቸው÷ ከዞኑ ስምንት ወረዳ ነዋሪዎች ከ6 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር በላይ መሰብሰቡን ገልፀዋል፡፡
ከዚህ ውስጥም በ3 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር 134 ሰንጋ፣ 156 ፍየልና 10 በጎችን በመግዛት እንዲሁም 3 መኪና ደረቅ ምግብ ድጋፍ መደረጉን ተናግረዋል፡፡
ድጋፉን ማዕከላዊ ጎንደር የሚገኘው የሎጀስቲክ ስምሪት ይረከባልም ነው ያሉት አቶ አንማው፡፡
ዞኑ ከዚህ በፊትም መሰል ድጋፍ ማድረጉንም አስታውሰዋል፡፡
በናትናኤል ጥጋቡ