Fana: At a Speed of Life!

ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የሚጠበቁባቸው የፍጻሜ ውድድሮች ዛሬ ይካሄዳሉ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 13፣2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በቻይና ናንጂንግ እየተካሄደ በሚገኘው 20ኛው የዓለም የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የሚጠበቁባቸው ሁለት የፍጻሜ ውድድሮች ዛሬ ይካሄዳሉ።

በዚህ መሰረትም ከቀኑ 8 ሰዓት ከ15 ላይ በሴቶች 3 ሺህ ሜትር የፍጻሜ ውድድር አትሌት ፍሬወይኒ ሃይሉ እና አትሌት ብርቄ ሃየሎም ይወዳደራሉ።

በተመሳሳይ በወንዶች 3 ሺህ ሜትር የፍጻሜ ውድድር አትሌት በሪሁ አረጋዊ፣ አትሌት ጌትነት ዋለ እና አትሌት ቢኒያም መሐሪ ከቀኑ 8 ሰዓት ከ33 ላይ ውድድራቸውን የሚያካሂዱ ይሆናል፡፡

በሁለቱም ጾታ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ለሜዳልያ ከወዲሁ ከፍተኛ ግምት የተሰጣቸው መሆኑን የፌደሬሽኑ መረጃ ያመላክታል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.