ሸገር ከተማ የሐይማኖቶች እኩልነት መገለጫ ናት – ተሾመ አዱኛ (ዶ/ር)
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 12፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የረመዳን ጾምን ምክንያት በማድረግ በሸገር ከተማ አሥተዳደር ኮዬ ፈጨ ክፍለ ከተማ የጎዳና ላይ የኢፍጣር መርሐ-ግብር ተካሄደ፡፡
በመርሐ-ግብሩ ላይም፤ የሸገር ከተማ ከንቲባ ተሾመ አዱኛን (ዶ/ር) ጨምሮ የከተማዋ እና የክፍለ ከተማው አመራሮች እንዲሁም የእስልምና እና የተለያዩ ሐይማኖቶች ተከታዮች ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል፡፡
የሸገር ከተማ አሥተዳደር ከንቲባ ተሾመ አዱኛን (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር፤ ሸገር የሐይማኖቶች እኩልነት ተምሳሌት እና ወንድማማችነት መገለጫ ናት ብለዋል፡፡