Fana: At a Speed of Life!

በሳዑዲ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ ከ3 ሺህ በላይ ወገኖች ወደ ሀገራቸው ተመለሱ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 12፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በሳዑዲ ዓረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ 3 ሺህ 416 ኢትዮጵያውያን በዚህ ሣምንት ወደ ሀገራቸው መመለሳቸውን የሴቶችና ማኅበራዊ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

እነዚህ ወገኖች ወደ ሀገራቸው የተመለሱት በሳምንቱ ውስጥ በተደረጉ ዘጠኝ በረራዎች መሆኑን የሚኒስቴሩ መረጃ አመላክቷል፡፡

ከተመለሱት መካከልም 2 ሺህ 859 ወንዶች ሲሆኑ ቀሪዎቹ ሴቶች ናቸው ተብሏል፡፡

በ4ኛው ዙር በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ 50 ሺህ ዜጎችን ለመመለስ ታቅዶ መጋቢት 3 ቀን  2017 በይፋ መጀመሩን መረጃው አስታውሷል፡፡

ይህን ተከትሎም እስከ አሁን 3 ሺህ 416 ኢትዮጵያውያንን ወደ ሀገር መመለስ መቻሉ ነው የተገለጸው፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.