በ1 ሺህ 500 ሜትር ጉዳፍ ጸጋይና ድርቤ ወልተጂ ለፍጻሜ አለፉ
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 12፣2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ20ኛው የዓለም የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ሻምፒዮና በሴቶች 1 ሺህ 500 ሜትር ጉዳፍ ጸጋይና ድርቤ ወልተጂ ለፍጻሜ አለፉ፡፡
በቻይና ናንጂንግ እየተካሄደ በሚገኘው ሻምፒዮና፥ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የተሳተፉበት የሴቶች 1 ሺህ 500 ሜትር ግማሽ ፍፃሜ ውድድር ተካሂዷል፡፡
በምድብ 1 የተሳተፈችው አትሌት ጉዳፍ ጸጋይ በ4 ደቂቃ ከ11 ሰከንድ ከ87 ማይክሮ ሰከንድ 1ኛ በመውጣት ለፍጻሜ ማለፍ ችላለች፡፡
በምድብ 3 የተሳተፈችው ሌላኛዋ አትሌት ድርቤ ወልተጂ ደግሞ በ4 ደቂቃ ከ12 ሰከንድ ከ25 ማይክሮ ሰከንድ በተመሳሳይ 1ኛ በመውጣት ፍጻሜውን ተቀላቅላለች፡፡