Fana: At a Speed of Life!

በክልሉ በ2 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር የሚከናወነው የቢሮ ሕንጻ ግንባታ ተጀመረ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 12፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) የቦንጋ ብዝሃ ማዕከል የክልል ተቋማትና የርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት ቢሮ ሕንጻ ግንባታን አስጀምረዋል፡፡

ርዕሰ መስተዳድሩ በዚህ ወቅት÷የሕንጻ ግንባታው የመንግስትን አገልግሎት በአንድ ማዕከል መስጠት እንደሚያስችል ተናግረዋል፡፡

ለግንባታው 2 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር በጀት መያዙን ገልጸው÷በሁለት ዓመት ጊዜ ውስጥ ተጠናቅቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ የቅርብ ክትትል ይደረጋል ነው ያሉት፡፡

ለአካባቢው ሕብረተሰብ የሥራ ዕድል፣ የቴክኖሎጂና የዕወቀት ሽግግር ከመፍጠር ረገድ ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳለው መጠቆማቸውንም የክልሉ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.