በዓለም የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ሻምፒዮና የሚሳተፈው የኢትዮጵያ ቡድን ወደ ቻይና አቀና
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 10፣2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በፈረንጆቹ ከመጋቢት 21 እስከ 23 ቀን 2025 በዓለም የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ የሚሳተፈው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ቡድን ወደ ቻይና ናንጂንግ ሌሊት ላይ አቅንቷል።
ቡድኑ 12 አትሌቶች፣ ሁለት አሰልጣኞች፣ አንድ ቡድን መሪ፣ አንድ የቴክኒክ ቡድን መሪ፣ አንድ ከፍተኛ የህክምና ባለሙያ እና አንድ ፊዝዮቴራፒስት ያካተተ ነው።
የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዲኤታ መኪዩ መሀመድ እና የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ኮማንደር አትሌት ስለሺ ስህንጨምሮ ሌሎች የፌዴሬሽኑ አመራሮች ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ በመገኘት ለቡድኑ ሽኝት ማድረጋቸውን የፌዴሬሽኑ መረጃ ያመላክታል።