ሳዑዲ ለማኅበራዊ ችግር ተጋላጭ ኢትዮጵያውያን 50 ቶን ቴምር ድጋፍ አደረገች
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 9፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የሳዑዲ ዓረቢያ መንግሥት ለማኅበራዊ ችግር ተጋላጭ ኢትዮጵያውያን የሚውል 50 ቶን ቴምር ድጋፍ ማድረጉን የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
ከተለያዩ አጋር አካላት ጋር በመተባበር ሀብት በማሰባሰብ የማኅበራዊ ድጋፍ ለሚሹ ወገኖች ተደራሽ የማድረግ ሥራ እየሠራ መሆኑን ሚኒስቴሩ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጹ ገልጿል፡፡