Fana: At a Speed of Life!

የታንዛኒያው ቻማ ቻ ማፒንዱዚ (ሲ ሲ ኤም) ፓርቲ ዋና ፀሃፊ ኢማኑኤል ኔቼንቤ (ዶ/ር) አዲስ አበባ ገቡ

አዲስ አበባ፣ ጥር 22፣ 2017 (ኤፍኤም ሲ) ዋና ፀሃፊው ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የግብርና ሚኒስትሩ ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) እና በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የፐብሊክ ዲፕሎማሲ ዳይሬክተር ጄነራል አምባሳደር ሽብሩ ማሞ አቀባበል አድርገውላቸዋል፡፡

የብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ ጉባዔ ከጥር 23 እስከ 25 ቀን 2017 ዓ/ም ድረስ “ከቃል እስከ ባሕል” በሚል መሪ ሃሳብ በአዲስ አበባ ይካሄዳል።

በጉባዔው ከ15 ሀገራት የተውጣጡ የጎረቤት ሀገራት እህት ፓርቲዎች እና የብሪክስ አባል ሀገራት እህት ፓርቲዎች 43 ከፍተኛ አመራሮች እንደሚታደሙ ይጠበቃል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.