የናይጄሪያው ኦል ፕሮግረሲቭ ኮንግረንስ (ኤ ፒ ሲ) ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበር አል ሀጂ አሊ ቡካር ዳሎሪ አዲስ አበባ ገቡ
አዲስ አበባ፣ ጥር 22፣ 2017 (ኤፍኤም ሲ) ምክትል ሊቀመንበሩ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ አቀባበል አድርገውላቸዋል።
የብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ ጉባዔ ከጥር 23 እስከ 25 ቀን 2017 ዓ/ም ድረስ “ከቃል እስከ ባሕል” በሚል መሪ ሃሳብ በአዲስ አበባ ይካሄዳል።
በጉባዔው ከ15 ሀገራት የተውጣጡ የጎረቤት ሀገራት እህት ፓርቲዎች እና የብሪክስ አባል ሀገራት እህት ፓርቲዎች 43 ከፍተኛ አመራሮች እንደሚታደሙ ይጠበቃል፡፡