Fana: At a Speed of Life!

በኦሮሚያ ክልል 93 ቢሊየን ብር ካፒታል ላስመዘገቡ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ተሰጠ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 11፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦሮሚያ ክልል ባለፉት ሶስት ወራት 93 ቢሊየን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ 4 ሺህ 316 ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መስጠቱን የክልሉ ኢንቨስትመንትና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ አስታውቋል፡፡
የቢሮው ሃላፊ አቶ አሕመድ እንድሪስ እንዳሉት÷በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ባለሃብቶች በክልሉ መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ በትኩረት ተሰርቷል፡፡
በዚህ መሰረትም 93 ቢሊየን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ 4 ሺህ 316 ባለሃብቶች በተለያዩ ዘርፎች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መውሰዳቸውን ጠቁመዋል፡፡
ባለሃብቶች በፍጥነት ወደ ሥራ እንዲገቡ አአስፈላጊው ክትትት እየተደረገ መሆኑንም ሃላፊው ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ተናግተዋል፡፡
በፀሃይ ጉሉማ

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.