Fana: At a Speed of Life!

የፕሪሚየር ሊጉ 4ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ከነገ ጀምሮ ይቀጥላል

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 8፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የ2017 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 4ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ከእረፍት መልስ ከነገ ጀምሮ በድሬዳዋ ስታዲየም በሚደረጉ ጨዋታዎች ይቀጥላል፡፡

በዚሁ መሠረት ነገ 10 ሠዓት ላይ ሀዲያ ሆሳዕና ከሐዋሳ ከተማ እና ምሽት 1 ሠዓት ላይ መቐለ 70 እንደርታ ከመቻል የሚጫወቱ ይሆናል፡፡

እንዲሁም ከነገ በስቲያ 10 ሠዓት ላይ ስሑል ሽረ ከድሬዳዋ ከተማ ሲጫወቱ በዚሁ ዕለት ምሽት 1 ሠዓት ላይ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ክለብ ጋር ይፋለማሉ፡፡

የ4ኛ ሣምንት መርሐ-ግብር ሲቀጥል የፊታችን ሰኞ ወላይታ ድቻ ከኢትዮጵያ ቡና እንዲሁም አዳማ ከተማ ከፋሲል ከነማ ይጫወታሉ፡፡

ማክሰኞ ዕለት ደግሞ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከባሕር ዳር ከተማ እና ኢትዮጵያ መድን ከሲዳማ ቡና ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.