Fana: At a Speed of Life!

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተለያዩ ሹመቶችን ሰጡ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 8፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዛሬው ዕለት ለሦስት ከፍተኛ ኃላፊነቶች ሹመቶችን ሰጥተዋል፡፡

በዚሁ መሠረት ጌዲዮን ጢሞቲዮስ (ዶ/ር) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፣ ሰላማዊት ካሳ የቱሪዝም ሚኒስትር እንዲሁም ሃና አርዓያሥላሴ የፍትሕ ሚኒስትር ሆነው በጠቅላይ ሚኒስትሩ ተሹመዋል፡፡

በቅርቡ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሆነው በተሰየሙት ታዬ አፅቀ ሥላሴ ቦታ የተተኩት ጌዲዮን ጢሞቲዮስ (ዶ/ር) የፍትሕ ሚኒስትር በመሆን ሲያገለግሉ ቆይተዋል፡፡

በሌላ በኩል ሰላማዊት ካሳ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴዔታ እንዲሁም ሃና አርዓያሥላሴ ደግሞ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ሆነው ሲያገለግሉ መቆየታቸው ይታወቃል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.