Fana: At a Speed of Life!

እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎች ባህር ዳርን ወደተሻለ የከተማነት ደረጃ የሚያሸጋግሩ ናቸው – ም/ጠ/ሚ ተመስገን ጥሩነህ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 2፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በከተማዋ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎች ባህር ዳርን ወደተሻለ የከተማነት ደረጃ የሚያሸጋግሩ እና የነዋሪዎችን ህይወት የሚያሻሽሉ ናቸው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ፡፡

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራ ትስስር ገጻቸው÷ ብርቱ እጆች፣ የማይዝሉ ክንዶች እና የሚያሰላስሉ አዕምሮዎች የዕድገት አየር የሚነፍስባቸውን ከተሞች ይገነባሉ ብለዋል፡፡

ዛሬ በባህር ዳር ከተማ እየተገነቡ የሚገኙ የቱሪስት መዳረሻዎችንና የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችን መጎብኘታቸውን ገልጸው፤ በከተማዋ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎች ባህር ዳርን ወደተሻለ የከተማነት ደረጃ የሚያሸጋግሩ እና የነዋሪዎችን ህይወት የሚያሻሽሉ ናቸው ብለዋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.