Fana: At a Speed of Life!

ኢሬቻ አብሮነትን  የሚያጎለብት በዓል ነው- የሐረሪ ክልል

አዲስ አበባ፣ መስከረም 24፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢሬቻ አንድነትን፣ አብሮነትን እና መተባበርን የሚያጎለብት በዓል መሆኑን የሐረሪ ክልላዊ መንግሥት ገለጸ፡፡

የክልሉ መንግሥት የኢሬቻ በዓልን በማስመልከት ባስተላለፈው የእንኳን አደረሳችሁ የመልካም ምኞት መግለጫ መልዕክት÷ ኢሬቻ ከክረምት ወደ በጋ፣ ከጨለማ ወደ ብርሃን መሸጋገርን በማሰብ ለፈጣሪ ምስጋና ለማቅረብ የሚከበር የዐደባባይ በዓል ነው ብሏል።

ኢሬቻ ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ሀብት ከመሆኑም ባሻገር÷ አንድነትን፣ አብሮነትን እና መተባበርን የሚያጎለብት በዓል መሆኑንም ገልጿል፡፡

በዓሉ የሕዝቦችን ትስስር የሚያጠናክር እና የሀገር ውስጥ ቱሪዝምን የሚያሳድግ መሆኑንም ነው የገለጸው፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.