Fana: At a Speed of Life!

አቶ እንዳሻው ጣሰው ከመከላከያ ሠራዊት ከፍተኛ አመራሮችና ጄኔራል መኮንኖች ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 21፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻዉ ጣሰዉ ከኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ከፍተኛ አመራሮች እና ጄኔራል መኮንኖች ጋር በጽህፈት ቤታቸዉ ተወያይተዋል፡፡

ውይይቱ አሁናዊውን ክልላዊ የፀጥታ ሁኔታ መገምገም እና የፀጥታ ሁኔታዉ ተጠናክሮ በሚቀጥልበት አቅጣጫ ላይ ያተኮረ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡

በውይይቱ ላይ የክልሉ ፀጥታና ሠላም ግንባታ ቢሮ ኃላፊ ተመስገን ካሳን ጨምሮ ሌሎችም የቢሮዉ ከፍተኛ አመራሮች መገኘታቸውን የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡

 

 

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.