Fana: At a Speed of Life!

አፈ-ጉባዔ አገኘሁ ተሻገር በካናዳ የሥራ ጉብኝት አደረጉ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 17፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ አገኘሁ ተሻገር በካናዳ የሁለት ቀናት የሥራ ጉብኝት አድርገዋል፡፡

በጉብኝታቸው ከካናዳ ምክር ቤት አፈ -ጉባዔ ጌርግ ፈርጉሰን እና ከሌሎች የመንግስት ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች ጋር በሁለቱ ሀገራት ግንኙነት ዙሪያ መክረዋል፡፡

በተጨማሪም በኢትዮጵያና ካናዳ የፌዴራል ሥርዓትና አሰራር ዙሪያ የተወያዩ ሲሆን÷ በዚህም በሀገራቱ ምክር ቤቶች መካከል ያለውን ትብብር ማጠናከር እንደሚገባ ተጠቁሟል።

ካናዳ በኢኮኖሚ ልማትና ሰብዓዊ መስኮች ለኢትዮጵያ እያደረገች ለሚገኘው ድጋፍ አፈ-ጉባዔ አገኘሁ ምስጋና አቅርበዋል፡፡

በቀጣይ በቴክኖሎጂ፣ በንግድ እና ኢንቨስትመንት ዘርፎች የሀገራቱን ግንኙነት ለማስፋት እንደሚሰራም ተናግረዋል።

አዳዲስ የትብብር መስኮችን ለመለየት 8ኛ የኢትዮ- ካናዳ የፓለቲካ ምክክር መድረክ በቅርብ ጊዜ ማካሄድ አስፈላጊ እንደሆነ መጠቀሱንም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.