Fana: At a Speed of Life!

የመስቀል ደመራና ኢሬቻ በዓላት ያለምንም የጸጥታ ችግር እንዲከበሩ ዝግጅት ተደርጓል – ቢሮው

አዲስ አበባ፣ መስከረም 12፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የመስቀል ደመራና ኢሬቻ በዓላት ያለምንም የጸጥታ ችግር እንዲከበሩ አስፈላጊው ዝግጅት መደረጉን የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ አስታውቋል።

የቢሮው ሃላፊ ሊዲያ ግርማ÷ባዓላቱ ባሕላዊ እና መንፈሳዊ እሴታቸውን ጠብቀው ያለምንም የጸጥታ ችግር እንዲከበሩ ተጨማሪ 11 ሺህ የሰላም ሰራዊት ማሰልጠን መቻሉን ተናግረዋል።

ከከተማው ሁሉም ክ/ከተሞች የተውጣጡ የሰላም ሰራዊት አባላት ጋር በፀጥታ ሥራ ዙሪያ ውይይት በማድረግ ስምሪት መሰጠቱን ጠቅሰዋል፡፡

የሰላም ሰራዊቱ እና የጸጥታ መዋቅሩ በጋራ በሰሩት ሥራ ከተማዋ ሰላሟ የተረጋገጠ መሆኑን ጠቁመው÷ከዚህ በላይ ለጸና ከተማዊ ሰላም ሁሉም በጋራ ሊሰራ እንደሚገባ አሳስበዋል።

በተለይም የመሰቀል ደመራና ኢሬቻ በዓላት በደማቅ ሁኔታ ተከብረው እንዲጠናቀቁ የከተማው ሕዝብ በሃላፊነት ሊሰራ እንደሚገባ ሃላፊዋ አስገንዝበዋል።

 

 

በይስማው አደራው

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.