Fana: At a Speed of Life!

የሂዝቦላ ከፍተኛ አዛዥ የሆነው ኢብራሂም አቂል ተገደለ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 10፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በሊባኖስ ቤሩት ውስጥ እስራኤል በሰነዘረችው የአየር ጥቃት የሂዝቦላ ከፍተኛ አዛዥ የሆነው ኢብራሂም አቂል መገደሉ ተነገረ።

እስራኤል የሂዝቦላ ቡድን ከፍተኛ አዛዥ የሆነውን ኢብራሂም አቂልን ዒላማ አድርጋ የአየር ጥቃቱን መፈጸሟን የሊባኖስ የደህንነት ምንጮች እና የእስራኤል ጦር ራዲዮ ገልጸዋል።

በዚህም ከአዛዡ በተጨማሪ ስምንት ሰዎች የተገደሉ ሲሆን ሌሎች 59 ሰዎች ደግሞ መቁሰላቸውን የሊባኖስ ጤና ሚኒስቴር መግለጹን ጠቅሶ ሬውተርስ ዘግቧል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.