Fana: At a Speed of Life!

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ አቴንስ የሚያደርገውን ሣምንታዊ በረራ ከፍ አደረገ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 8፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከኅዳር 23 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ግሪክ ዋና ከተማ አቴንስ በሣምንት ሥድስት ቀን ለመብረር የሚስችለውን ዝግጅት ማጠናቀቁን አስታወቀ፡፡

ሣምንታዊ የበረራ ቁጥሩን ከፍ ከማድረጉ በፊት ወደ አቴንስ የሚያደርገው ሣምንታዊ በረራ አራት ጊዜ እንደነበርም ነው አየር መንገዱ በማኅበራዊ ትስስር ገጹ ያስታወቀው፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.