Fana: At a Speed of Life!

ኢትዮጵያ የካፍ ጠቅላላ ጉባዔን እንድታስተናግድ ተወሰነ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 6፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ባደረገው ስብሰባ የካፍ ጠቅላላ ጉባዔ በኢትዮጵያ እንዲካሄድ ወሰነ፡፡

ጉባዔው በኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ እንዲካሄድ ታስቦ የነበረ ቢሆንም÷ ሀገሪቱ ማስተናገድ እንደማትችል ማሳወቋን ተከትሎ ኢትዮጵያ ጉባዔውን ለማካሄድ ያቀረበችውን ጥያቄ ካፍ አጽድቋል፡፡

በዚህም መሰረት የካፍ ጠቅላላ ጉባዔ በጥቅምት ወር በአዲስ አበባ ከተማ እንደሚካሄድ መገለጹን የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን መረጃ አመላክቷል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.