Fana: At a Speed of Life!

በሲድኒ ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ተከታትለው በመግባት አሸነፉ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 5፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በአውስትራሊያ ሲድኒ ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ተከታትለው በመግባት አሸነፉ።

በዓለም አትሌቲክስ የፕላቲኒየም ደረጃ በተሰጠው በሲድኒ ማራቶን አትሌት ወርቅነሽ ኢዴሳ 2:21:40 በሆነ ሰዓት በመግባት የቦታውን ክብረ ወሰን በማሻሻል ጭምር ውድድሩን አሸንፋለች።

አትሌት ሩቲ አጋ 2:23:09 እንዲሁም አትሌት ጎይተቶም ገብረሥላሴ 2:24:16 በሆነ ሰዓት በመግባት ሁለተኛ እና ሶስተኛ ደረጃ በመያዝ ውድድሩን አጠናቀዋል።

በወንዶች ደግሞ ኬኒያዊው አትሌት ብሪሚን ሚሶይ 2:06:17 በሆነ ሰዓት በመግባት ውድድሩን ሲያሸንፍ፤ ኢትዮጰያዊው አትሌት ጫሉ ደሶ 2:08:01 በመግባት ውድድሩን ሁለተኛ ሆኖ አጠናቋል።

በውድድሩ ብርቱ ፉክክር ሲያደርጉ የነበሩት አትሌት ልዑል ገብረስላሴ እና ታዱ አዳቴ ስድስተኛ እና ሰባተኛ ደረጃን ይዘው ውድድሩን ጨርሰዋል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.