Fana: At a Speed of Life!

የመውሊድ በዓል በታላቁ አንዋር መስጂድ እየተከበረ ነው

አዲስ አበባ ፣ መስከረም 5፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) 1 ሺህ 499ኛው የመውሊድ በዓል በታላቁ አንዋር መስጂድ እየተከበረ ይገኛል።

በዓሉ የሐይማኖት አባቶች፣ የእምነቱ ተከታዮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ከማለዳው ጀምሮ በተለያዩ ሐይማኖታዊ ስነ-ስርዓቶች በመከበር ላይ ነው።

በአንዋር መስጂድ እየተከበረ ያለውን በዓል የታላቁ አንዋር መስጂድ ኢማም ሸህ ጣኻ ሀሩን ቁርአን በመቅራትና ዱዓ በማድረግ በይፋ የሚያስጀምሩት ይሆናል።

በዓሉ በሀገር አቀፍ ደረጃ በታላቁ አንዋር መስጂድ በሰደቃ፣ በመንዙማና በነሺዳ በሀይማኖት አባቶች በወጣቶች እና በታዳጊዎች መርሐ ግብር እንደሚከበር ኢዜአ ዘግቧል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.