Fana: At a Speed of Life!

በክልሉ በ2017 ከ10 ሚሊየን በላይ ተማሪዎች የምገባ አገልግሎት ተጠቃሚ ይሆናሉ ተባለ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 4፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በ2017 የትምህርት ዘመን 10 ነጥብ 1 ሚሊየን ተማሪዎች የትምህርት ቤት ምገባ አገልግሎት ተጠቃሚ እንደሚሆኑ የኦሮሚያ ክልል ትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ ግርማ ባይሳ ገለጹ፡፡

የተማሪዎች የምገባ መርሐ-ግብር የትምህርት ተሳትፎና የውጤታማነት ችግሮች መፍቻ እየሆነ መምጣቱን ገልጸው÷  ይህን ታሳቢ በማድረግ በተጠናከረ መልኩ እየተተገበረ ነው ብለዋል፡፡

በዘንድሮው ትምህርት ዘመንም በ20 ሺህ ትምህርት ቤቶች 10 ነጥብ 1 ሚሊየን የቅድመ መደበኛና 1ኛ ደረጃ ተማሪዎች የትምህርት ቤት ምገባ አገልግሎት ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ለኢዜአ ተናግረዋል፡፡

በትምህርት ቤቶች ለመማር ማስተማር አገልግሎት የማይውሉ ቦታዎችን በተቀናጀ ግብርና የማልማት ስራ እንደሚከናወንም አመላክተዋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.