Fana: At a Speed of Life!

በቢሾፍቱ እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት የቱሪስት መስኅብነቷን ይጨምራል – ከንቲባ አዳነች

አዲስ አበባ፣ መስከረም 3፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በቢሾፍቱ ከተማ እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት ሥራ ሲጠናቀቅ የቱሪስት መስኅብነቷን በይበልጥ እንደሚጨምር የአዲስ አበባ ከተማ አሥተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሰጡት የሥራ መመሪያ መሠረት ከንቲባዋ በቢሾፍቱ ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የኮሪደር ልማት ሥራዎችን መጎብኘታቸውን በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ገልጸዋል፡፡

ከጉብኝታቸው ጎንለጎንም ከከተማዋ አመራሮች፣ ከነዋሪ ተወካዮች ፣ ከተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች ጋር በተያዙ እቅዶች እና በቅንጅት በሚሰራበት ሁኔታ  ላይ መምከራቸውን ነው የገለጹት፡፡

የኮሪደር ልማቱ በከተማዋ በአምስት አካባቢዎች እየተከናወነ መሆኑን በመግለጽ÷ ይህም የመንገድ፣ የእግረኛና የብስክሌት መንገድ፣ የሕዝብ መዝናኛ ፓርክ እና መንገዶችን የማስዋብ ተግባራትን እንደሚያካትት አመላክተዋል፡፡

እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት ሥራ ሲጠናቀቅም በይበልጥ የቱሪስት መስኅብነቷን ይጨምራል፤ የከተማዋን የወደፊት ዕድልም ከፍ ያደርጋል ብለዋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.