Fana: At a Speed of Life!

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ለ2 ሺህ 144 የህግ ታራሚዎች ይቅርታ አደረገ

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 1፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አዲሱን ዓመት ምክንያት በማድረግ ለ2 ሺህ 144 የህግ ታራሚዎች ይቅርታ ማድረጉን አስታወቀ፡፡

የክልሉ ፍትህ ቢሮ ኃላፊ እሸቱ ጎዴቶ÷ ይቅርታ የተደረገላቸው የህግ ታራሚዎች በማረሚያ ቤት ቆይታቸው መልካም ሥነ-ምግባር ያሳዩ እና በህግ የተደነገገውን የይቅርታ መሥፈርት የሚያሟሉ መሆናቸውን ተናግረዋል።

ከይቅርታ ተጠቃሚዎች ውስጥ 43 የህግ ታራሚዎች ሴቶች ሲሆኑ ከእነሱ ጋር በማረሚያ ቤት ውስጥ የሚገኙ 7 ህፃናትም የይቅርታው ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡

አንድ የህግ ታራሚ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት በማምጣቱ በልዩ ሁኔታ የይቅርታ ተጠቃሚ መሆኑን መግለጻቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን መረጃ አመልክቷል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.