Fana: At a Speed of Life!

አትሌት ያየሽ ጌቴ ክብረወሰን በማሻሻል ጭምር አሸነፈች

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 27፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ17ኛው የፓራሊምፒክ ውድድሮች አትሌት ያየሽ ጌቴ በ1 ሺህ 500 ሜትር ሴቶች የዓይነ ስውር (T-11) ፍጻሜ ክብረ ወሰን በማሻሻል ጭምር አሸነፈች፡፡
አትሌቷ ቀደም ሲል 4 ደቂቃ ከ27 ሰከንድ ከ68 ማይክሮ ሰከንድ በራሷ ተይዞ የነበረውን የዓለም ክብረ ወሰን በአራት ሰከንድ በማሻሻል አንደኛ ደረጃን ይዛ ማጠናቀቅ ችላለች።
ማሸነፏን ተከትሎም ሁለተኛውን የወርቅ ሜዳሊያ ለሀገሯ ማስገኘቷን ኢዜአ ዘግቧል፡፡
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.