Fana: At a Speed of Life!

4 ነጥብ 6 ኪሎግራም ወርቅ ይዞ ሲንቀሳቀስ የነበረ ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር ዋለ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 2፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) 4ነጥብ 6 ኪሎ ግራም ወርቅ በሕገ-ወጥ መንገድ ይዞ ሲንቀሳቀስ የነበረውን ተጠርጣሪ ከኤግዚቢቱ ጋር በቁጥጥር ሥር ማዋሉን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ገለፀ፡፡

ተጠርጣሪው በዛሬው ዕለት በአሶሳ ከተማ 02 ቀበሌ በሃይሉክስ መኪና 4 ነጥብ 6 ኪሎ ግራም ወርቅ ጭኖ ሲንቀሳቀስ የፌዴራል ፖሊስ ኮንትሮባንድ ቁጥጥር መምሪያ ከኢትዮጵያ ጉሙሩክ ኮሚሽን ጋር በመተባበር ባደረጉት ጠንካራ ክትትል በቁጥጥር መዋሉ ነው የተገለጸው፡፡

ኅብረተሰቡ ህገ-ወጥ የወርቅ ንግድንና ዝውውር በሀገር ኢኮኖሚ ላይ የሚያስከትለውን ጉዳት በመገንዘብ መሰል ተግባር ላይ የተሰማሩ ግለሰቦችና ቡድኖችን ሲመለከት ጥቆማ እንዲሰጥ የፌዴራል ፖሊስ ጥሪ ማቅረቡን ከገጹ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.