Fana: At a Speed of Life!

ከንቲባ አዳነች አቤቤ የምሽት ፈረቃ የኮሪደር ልማት ሰራተኞችን አበረታቱ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 24፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ የምሽት ፈረቃ የኮሪደር ልማት ሰራተኞችን አበረታቱ፡፡

ከንቲባዋ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ÷አዲስ አበባን እያስዋቡና እያደሱ የሚገኙ ሰራተኞችን በመዘዋወር የሚከናውኗቸውን የሥራ ሂደቶች መመልከታቸውን አንስተዋል፡፡

የሰራተኞችን የሥራ ሂደት ከመገምገም ባለፈ የሌሊት ፈረቃ ሥራ የሚያከናውኑ ሰራተኞችን እራት በመጋበዝ በሥራቸው ይበልጥ እንዲነሳሱ ማበረታታቸውን ገልጸዋል፡፡

በዚህ ፕሮጀክት የሚተጉ ሰራተኞችን በመመገብና በማበረታታት ላይ የሚገኙ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎችንም አመስግነዋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.