አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ ከቤላሩስ አምባሳደር ጋር ተወያዩ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 14፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ በኢትዮጵያ የቤላሩስ አምባሳደር ፓርቬል ቪዚያትኪ ጋር ተወያይተዋል፡፡
በውይይታቸውም÷ መደበኛ የፖለቲካ ምክክር በማካሄድ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት የበለጠ ለማጠናከር ተስማምተዋል።
ኢትዮጵያና ቤላሩስ በኢኮኖሚ፣ ንግድ፣ ግብርና፣ ትምህርት እና በአየር ትራንስፖርት ዘርፎች ያላቸውን ግንኙነት ማሳደግ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መምከራቸውንም የሚኒስቴሩ መረጃ ያመላክታል፡፡