Fana: At a Speed of Life!

በአዲስ አበባ ከነገ ጀምሮ የ6ኛ ክፍል ፈተና ይሰጣል

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 11፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ከነገ ጀምሮ እስከ ሰኔ 14 ቀን 2016 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል ፈተና እንደሚሰጥ የአዲስ አበባ ከተማ አሥተዳደር ትምህርት ቢሮ አስታወቀ፡፡

ቢሮው እንዳስታወቀው÷ በ183 የመፈተኛ ጣቢያዎች ለ86 ሺህ 222 ተማሪዎች ፈተናው ይሰጣል፡፡

በፈተና ጣቢያዎቹም ከ2 ሺህ 200 በላይ ፈታኞች፣ ከ700 በላይ ሱፐር ቫይዘሮች፣ 183 የፈተና ጣቢያ ኃላፊዎች ፈተናውን ለማስፈጸም መመደባቸውን የቢሮው መረጃ አመላክቷል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.