Fana: At a Speed of Life!

1ነጥብ 8 ሚሊየን ሄክታር መሬት በበቆሎ ለመሸፈን አቅደን እየሰራን ነው-አቶ ሽመልስ አብዲሳ

 

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 7፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በዚህ ዓመት እንደ ክልል 1ነጥብ 8 ሚሊየን ሄክታር መሬት በበቆሎ ለመሸፈን አቅደን በመስራት ላይ እንገኛለን ሲሉ የኦሮሚያ ክልል ርእሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ ተናገሩ፡፡

ከዚህ ውስጥ ሁለቱ የጉጂ ዞኖች ከዓመቱ የክልሉ የበቆሎ እርሻ ዕቅድ 17 በመቶ ወይም 300 ሺህ ሄክታር ገደማ ድርሻ አላቸው ሲሉ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው አስፈርዋል።

በሁለቱ የጉጂ ዞኖች እስካሁን 280 ሺህ ሄክታር ወይም 94 በመቶ መሬት በበቆሎ የተሸፈነ ሲሆን÷ እንደክልል ያለው አፈጻጸምም 1 ነጥብ 7 ሚሊየን ሄክታር መሬት ወይም 95 በመቶ ደርሷል ብለዋል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.