Fana: At a Speed of Life!

አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ በኢትዮጵያ የግሪክ አምባሳደር ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 4፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ በኢትዮጵያ የግሪክ አምባሳደር አና ፋሩ ጋር ተወያይተዋል፡፡

በውይይታቸውም አምባሳደር ምስጋኑ ÷ ኢትዮጵያና ግሪክ በህዝብ ለህዝብ፣ በኢኮኖሚያዊና ፓለቲካዊ መስኮች ያላቸውን ግንኙነት ማሳደግ እንዳለባቸው ገልጸዋል፡፡

ለዚህም በሁለቱ ሀገራት መካከል መደበኛ የፖለቲካ ምክክር ማድረግ እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።

በተጨማሪም ሁለቱ ወገኖች በሀገራቱ ግንኙነት ውስጥ መሻሻል ስላለባቸው ጉዳዮችና ስለ ሌሎች የሁለትዮሽ ጉዳዮች መምከራቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.