Fana: At a Speed of Life!

የአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ አባላት ኮንፈረንስ እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 21፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ አባላት ኮንፈረንስ በባሕር ዳር ከተማ እየተካሄደ ነው፡፡

በኮንፈረንሱ ላይ÷ የአማራ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ እና የክልሉ ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ፋንቱ ተስፋዬን ጨምሮ የፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች እና አባላት ተገኝተዋል፡፡

“ቃልን በተግባር ለኢትዮጵያ ብልጽግና” በሚል መሪ ሐሳብ እየተካሄደ የሚገኘው ኮንፈረንሱ÷ ከመጋቢት 21 እስከ 23 ቀን 2016 ዓ.ም እንደሚቀጥል ተገልጿል፡፡

በመድረኩም ባለፉት ሁለት ተኩል ዓመታት የክልሉን ሕዝብ ተጠቃሚ ለማድረግ የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት ላይ ውይይት ይደረጋል መባሉን በብልጽግና ፓርቲ አማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት መረጃ አመላክቷል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.