አምባሳደር ታዬ ከቡሩንዲ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር ተወያዩ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 7፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ ከቡሩንዲ አቻቸው አምባሳደር አልበርት ሽንግሮ ጋር ተወያይተዋል፡፡
በውይይታቸውም÷ በሀገራቱ የሁለትዮሽ እና ባለብዙ ወገን ጉዳዮች ላይ መክረዋል፡፡
ከዚህ ባለፈም የሀገራቱን ግንኙነት ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ መምከራቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመላክታል፡፡