Fana: At a Speed of Life!

አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በ2016 ዓ.ም በነባሩ ስርዓት መደበኛ ተማሪዎችን እንደሚቀበል ገለጸ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 10፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በ2016 ትምህርት ዘመን በነባሩ ስርዓት የመደበኛ ተማሪዎችን እንደሚቀበል አስታውቋል፡፡

የዩኒቨርሲቲው ተጠባባቂ ፕሬዚዳንት ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) ÷ በዩኒቨርሲቲው እየተከናወኑ የሚገኙ የማሻሻያ ስራዎችን አስመልክተው መግለጫ ሰጥተዋል።

በመግለጫቸውም÷ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ራስ ገዝ መሆኑን ተከትሎ የሽግግር ሒደት ላይ እንደሚገኝ አስረድተዋል፡፡

የሽግግር ሒደቱ እስኪጠናቀቅ ድረስም ነባር አሰራሮች ባሉበት እንደሚቀጥሉ ነው የተናገሩት፡፡

ዩኒቨርሲቲው የሚቀይራቸው አሰራሮች ሲኖሩም በየጊዜው የማሳወቅ ስራ እንደሚከናወን አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡

የዩኒቨርሲቲው የራስ ገዝነት ሽግግር ጊዜ ከአንድ ዓመት እስከ አንድ ዓመት ተኩል እንደሚጠናቀቅም ተጠባባቂ ፕሬዚዳንቱ ገልጸዋል፡፡

በዘቢብ ተክላይ

#Ethiopia
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.