Fana: At a Speed of Life!

አቶ ደመቀ መኮንን ከጣሊያን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ከጣሊያን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒዮ ታጃኒ፣ ከኤርትራና ከሶማሊ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ኦስማን ሳላህና አብሽር ኦማር ጋር ተወያይተዋል፡፡

78ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ “ሰላም፣ ብልጽግና፣ ለውጥና ዘላቂነት” በሚል መሪ ሀሳብ በኒው ዮርክ እየተካሄደ ነው።

ሚኒስትሮቹ ከጉባኤው ጎን ለጎን በሀገራቱ ኢንቨስትመንት፣በንግድ፣በሰላምና በፀጥታ ትብብር እና ሽብርተኝነትን መከላከል በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ መክረዋል፡፡

ለዚህም ÷ሚኒስትሮቹ ከጉዳዩን ወደ ተግባር ለመቀየር እንዲቻል የጋራ መድረክ እንዲኖራቸው መስማማታቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.