Fana: At a Speed of Life!

አቶ ደመቀ መኮንን ከኩባ ፕሬዚዳንት ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ ፣ መስከረም 5 ፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ከኩባ ፕሬዚዳንት ሚጉዌል ቤርሙዴዝ ጋር ተወያይተዋል።

የቡድን 77 እና ቻይና የመሪዎችና የመንግስታት ጉባዔ በኩባ ሀቫና ከተማ እየተካሄደ ነው።

አቶ ደመቀ÷ ከጉባኤው ጎን ለጎን ከኩባው ፕሬዚዳንት ሚጉዌል ቤርሙዴዝ ጋር መምከራቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል፡፡

በውይይታቸውም÷ የሁለቱን ሀገራት የሁለትዮሽ ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከርና በከፍተኛ ባለስልጣናት ደረጃ ጉብኝቶችን ለማድረግ ከስምምነት ላይ መድረሳቸው ተገልጿል፡፡

አቶ ደመቀ መኮንን÷ ከኩባ ምክትል ፕሬዚዳንት፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርና ከኩባ ፓርላማ አፈ-ጉባዔ ጋርም በተለየዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል፡፡

#Ethiopia
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.