Fana: At a Speed of Life!

11ኛው የዓመቱ በጎ ሰው ሽልማት ሥነ-ሥርዓት ተካሄደ

አዲስ አበባ ፣ ጳጉሜን 5 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) 11ኛው የዓመቱ በጎ ሰው ሽልማት ሥነ-ስርዓት በዛሬው ዕለት ተካሂዷል።

በሽልማት ስነ-ሥርዓቱ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደረጃ ቀና እንድትል ላደረጉ እና የተለያዩ በጎ ስራዎችን ላከናወኑ በጎ ሰዎች እውቅና ተሰጥቷል።

ባለፋት 10 ዓመታት በተደረጉ የበጎ ሰው እውቅና መስጫ ስነ-ሥርዓቶች 225 በጎ ዜጎች በተለያዩ ዘርፎች መሸለማቸው ተገልጿል፡፡

በዛሬው የበጎ ሰው ሽልማት ስነ-ሥርዓትም በተለያዩ ዘርፎች ላሸነፉ በጎ ሰዎች እና ተቋማት እውቅና ተሰጥቷል፡፡

በዚህ መሰረትም ፡-

• በመምህርነት ዘርፍ መምህር አዝማች ይርጋ ገብሬ

• በባህልና ቅርስና ቱሪዝም የኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ተቋም

• በንግድ ኢንዱስትሪና ስራ ፈጠራ ዘርፍ ኩሪፍቱ ሪዞርትና ስፓ

• በበጎ አድራጎት ዘርፍ ወይዘሮ እቴነሽ ወ/አገኘሁ ( የብርሀን ለህፃናት በጎ አድራጎት መስራችና ስራ አስኪያጅ)
• በኪነጥበብ ዘርፍ ሰአሊ ወርቁ ጎሹ

• መንግስታዊ የስራ ሀላፊነትን በአግባቡ በብቃት በመወጣት ዘርፍ ያየህይራድ ቅጣው (ዶ/ር)) (የትምህርት ሚንስትርና የብሄረሰብ ጥናት ኢንስቲትዩት ኃላፊ የነበሩ)

• በሚዲያና ጋዜጠኝነት ዘርፍ ጋዜጠኛ ኤፍሬም እንዳለ

• በሳይንስና ቴክኖሎጂ ዘርፍ ሙሉዓለም ገሰሰ (ዶ/ር)

• በትውልደ ኢትዮጵያውያን ዘርፍ አሰፋ ጀጃው (ዶ/ር) (የህክምና ባለሞያ በአሜሪካ የህክምና ድጋፍ ለሚፈልጉ ድጋፍ ያደረጉ) ተሸላሚ ሆነዋል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.