Fana: At a Speed of Life!

አዲስ ወግ የውይይት መድረክ ተካሄደ

አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 13፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) አዲስ ወግ የውይይት መድረክ “የክረምት ትጋት የዓመት ልማት” በሚል ርዕስ

ተካሂዷል፡፡

ተወያዮቹም የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ኃላፊና የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር አለምጸሐይ ጳውሎስ፣ የአረንጓዴ አሻራ የቴክኒክ ኮሚቴ አስተባባሪ አደፍርስ ወርቁ (ዶ/ር)፣ የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ ጀማል አህመድና የደጃዝማች ወንድይራድ የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ር/መምህር ሰለሞን ክቤ ናቸው፡፡

ዓለምጸሐይ ጳውሎስ በውይይት መድረኩ ላይ እንደገለጹት÷ በሀገር አቀፍ ደረጃ በሕዝቡ ተሳትፎ በክረምቱ በሁሉም ዘርፍ የተሰሩ ስራዎች ለበጋው መሰረት የጣሉ እና ጽናትን ያየንባቸው ናቸው ብለዋል ።

ከ20 ሚሊየን በላይ ወጣቶች በክረምቱ በበጎ ፈቃድ ስራ ተሰማርተው ማህበረሰቡን እንዳገለገሉ ጠቅሰው÷ የሌማት ትሩፋትም የሁሉም ቤተሰብ ስራ እየሆነ ይገኛል ነው ያሉት።

አደፍርስ ወርቁ (ዶ/ር) በበኩላቸው÷ የኢትዮጵያ ግማሽ ያህሉ የቆዳ ስፋት የተለያየ አይነት የመሬት መጎዳት እንደገጠመው አስረድተዋል፡፡

በአንድ ዓመት ብቻ በአፈር መከላት ምክንያት ኢትዮጵያ 4 ነጥብ 3 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ሃብት እንደምታጣ ጥናቶች እንደሚያመላክቱ አንስተዋል፡፡

የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብርም የምርትና ምርታማነት፣ ዘላቂ የልማት ግቦች፣ የስራ እድል ፈጠራ እንዲሁም የደን ሽፋን ጥያቄዎቻችንን በጋራ ለመመለስ ጅምር ሆኖናል ብለዋል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.