Fana: At a Speed of Life!

በመዲናዋ መንግስት ያለአግባብ ሊያጣው የነበረ 2 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር ማዳን ተችሏል

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 7፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መንግስት ያለአግባብ ሊያጣው የነበረ 2 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር በላይ ማዳን መቻሉን የከተማዋ ፍትሕ ቢሮ አስታውቋል፡፡

በቢሮው የሕግ ክትትል ዘርፍ ም/ሃላፊ አቶ ተስፋዬ ደጀኔ እንደገለጹት÷በ2015 በጀት ዓመት በመዲናዋ የተከሰቱ ብልሹ እና ሕገ ወጥ ተግባራትን ከመቅረፍ አንጻር በርካታ ስራዎች ተከናውነዋል፡፡

በከተማ አስተዳደሩ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 7 ሺህ 499 ክሶች እና የፍርድ ቤት ክርክሮች እንደነበሩ አቶ ተስፋዬ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ተናግረዋል፡፡

ከዚህ ውስጥም ቢሮው 2 ሺህ 497 መዝገቦችን በመከራከር በፍርድ ቤት ውሳኔ እንዲያገኙ ማድረጉን ነው የገለጹት፡፡

2 ሺ 266 መዝገቦች ለመንግስት እንዲወሰኑ ተደርጓል ያሉት ም/ሃላፊው÷ በዚህም መንግስት ሊያጣው የነበረ 2 ነጥብ 58 ቢሊየን ብር በላይ ማዳን ተቸሏል ብለዋል፡፡

በሌላ በኩል አምስት ትልልቅ ክርክሮችን በድርድር እንዲያልቁ በማድረግ መንግስት ያለአግባብ ሊያጣው የነበረ 299 ሚሊየን ብር ማዳን መቻሉን ጠቁመዋል፡፡

በመላኩ ገድፍ

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.