Fana: At a Speed of Life!

ከንቲባ አዳነች አቤቤ ከአዘርባጃን የፐብሊክ ሰርቪስ እና ሶሻል ኢኖቬሽን ሚኒስትር ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 25፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ከአዘርባጃን የፐብሊክ ሰርቪስ እና ሶሻል ኢኖቬሽን ሚኒስትር ኡልቪ ሜዲዬቭ እና ልዑካን ቡድናቸው ጋር ተወያዩ፡፡

በውይይታቸውም÷ዘመናዊ እና የተቀላጠፈ አገልግሎት በአንድ ማዕከል መስጠት በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ መክረዋል፡፡

በተጨማሪም ÷አዲስ አበባ ከተማን የሚመጥን አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል ምርጥ ተሞክሮ መካፈላቸውን ከንቲባ አዳነች በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሁፍ አስፍረዋል፡፡

በቀጣይ በትብብር ለመስራት በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ከስምምነት መድረሳቸውን ገልጸዋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.