Fana: At a Speed of Life!

በመንግስት ሰራተኞች አዲሱ የደመዎዝ ጭማሪ አፈጻጸም መመሪያ ላይ ውይይት ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 11፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን የመንግስት ሰራተኞች አዲሱ የደመዎዝ ጭማሪ አፈጻጸም መመሪያ ላይ ከክልልና ከተማ አስተዳደር ሲቪል ሰርቪስ ቢሮ ሃላፊዎች ጋር ተወያይቷል፡፡

በውይይት መድረኩ የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽነር መኩሪያ ሃይሌ (ዶ/ር)፣ የክልልና ከተማ አስተዳደር ሲቪል ሰርቪስ ቢሮ ሃላፊዎች እንዲሁም የሚመለከታቸው ባለሙያዎች ተሳትፈዋል፡፡

የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሺዴ የመንግስት ሠራተኞች አዲሱ ደመዎዝ ከጥቅምት ወር ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚደረግ ማስታወቃቸው ይታወሳል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.