Fana: At a Speed of Life!

ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ ከፈረንሳይ የልማት ድርጅት ተወካዮች ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 25፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በከተማና መሰረት ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ የተመራ ልዑካን ቡድን ከፈረንሳይ የልማት ድርጅት ተወካዮች ጋር ተወያይቷል፡፡

በውይይታቸውም÷ ለኢትዮጵያ ጠቃሚ የሆኑ ተጨማሪ የትብብር ፕሮጀክቶችን በጋራ መስራት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ መክረዋል፡፡

በተጨማሪም÷ እስካሁን በድርጅቱ የተከናወኑ የትብብር ሥራዎችም የሚበረታቱ መሆናቸው በውይይቱ መነሳቱን በፈረንሳይ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.