Fana: At a Speed of Life!

ድርጅቱ ኢኮኖሚውን ለማነቃቃት የኮንቴነርና የከባድ መኪና ግዢዎችን ሊፈጽም ነው

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 1፣ 2014(ኤፍ ቢ ሲ)በኮሮናና በውስጥ ሰላም እጦት የተዳከመውን ኢኮኖሚ ለማነቃቃት የሚያስችሉ የኮንቴነርና የከባድ መኪናዎችን ግዢ እንደሚፈጽም የኢትዮጵያ ባህር ትራንዚትና ሎጅስቲክ አገልግሎት ድርጅት አስታወቀ፡፡

የድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሮባ መገርሳ ለኢፕድ እንደተናገሩት÷ እንዲገዙ የተፈቀዱት ከባድ የጭነት ተሽከርካሪዎች ግዢ በኮሮናና በውስጥ ሰላም እጦት ጉዳት የደረሰበትን የኢትዮጵያን የገቢና ወጪ እንቅስቃሴ ለማሳላጥና ቶሎ እንዲያገግም ያስችላል፡፡

በሁሉም ዘርፍ ከውጭ የሚመጡና ከሀገር የሚወጡትን ግብዓቶች በተቀላጠፈ መልኩ ለማጓጓዝም ይረዳል፡፡

በ2014 በጀት ዓመትም የግብርና ምርት ማሳደጊያ የሚሆን የአፈር ማዳበሪያን በማጓጓዝ በኢትዮጵያ የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ የገለጹት ዋና ሥራ አስፈፃሚው÷ ድርጅቱ በተያዘው የበጀት ዓመት ከአሥር ሚሊየን ቶን በላይ የገቢና ወጪ ጭነቶችን ለማስተናገድ በዕቅድ መያዙን ተናግረዋል፡፡

በ2014 ዓመት የሚጓጓዘው የአፈር ማዳበሪያ ሁለት ሚሊየን ቶን ገደማ ሊደርስ እንደሚችል የጠቆሙት ዋና ሥራ አስፈጻሚው÷ ማዳበሪያ በተወሰነለት ጊዜ ግዥው ከተጠናቀቀ ድርጅቱ እንደ አስፈላጊነቱ በመርከብና በከባድ የጭነት ተሽከርካሪ ማጓጓዝ እንደሚጀምር ገልፀዋል፡፡

የማጓጓዝ ሂደቱን በማቀላጠፍም ለአርሶ አደሩ ማህበረሰብ ግብዓቱን በጊዜው እንዲደርስ አስፈላጊው ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን አመላክተዋል፡፡

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.