Fana: At a Speed of Life!

በአዋሽ ወልዲያ የባቡር ፕሮጀክት ላይ የሚገኙ ዋሻዎች ሥራ ተጠናቀቀ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 23፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በአዋሽ ወልዲያ የባቡር ፕሮጀክት ላይ የሚገኙ የ12ቱም ዋሻዎች ሥራ ሙሉ በሙሉ ተጠናቀው ለአገልግሎት ዝግጁ መሆናቸው ተገለጸ።
 
የ12ቱም ዋሻዎች አጠቃላይ ርዝመት ከ10 ኪሎ ሜትር በላይ ነው ተብሏል፡፡
 
ረዥሙ ዋሻ በወልዲያ አካባቢ የሚገኘው ሲሆን 2 ነጥብ 3 ኪሎ ሜትር ርዝመት ይሸፍናል፡፡
የፕሮጀክቱ ወቅታዊ የአፈጻጸም ደረጃም 91 ነጥብ 88 በመቶ መድረሱን ከትራንስፖርት ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.