የሀገር ውስጥ ዜና

የብልጽግና ፓርቲና የራሽያ ዩናይትድ ፓርቲ ግንኙነታቸው በሚጠናከርበት ዙሪያ መከሩ

By Feven Bishaw

November 15, 2021

 

አዲስ አበባ፣ ህዳር 6 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ አደም ፋራህ እና በኢትዮጵያ የሩሲያ ፌዴሬሽን አምባሳደር ኢቨጌኒ ቴረኺን የብልጽግና ፓርቲና የሩሲያ ዩናይትድ ፓርቲን ግንኙነት በሚጠናከርበት ዙሪያ ተወያይተዋል፡፡

ከዚህ ቀደም በፓርቲዎቹ መካከል የተፈረመውን የመግባቢያ ሰነድ መሰረት ባደረገ መልኩ የፓርቲ ለፓርቲ ግንኙነቱን ተግባራዊ ለማድረግ በሚያስችሉ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል።