ቢዝነስ

በኢትዮ ኬንያ ድንበር ማርሳቢት ግዛት ላይ ተጨማሪ የግብይይት ስፋራ ሊከፈት ነው

By Tibebu Kebede

February 10, 2020

አዲስ አበባ፣ የካቲት 2፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የንግድ እና የሰዎችን እንቅስቃሴ የበለጠ ለማሳደግ ከሞያሌ በተጨማሪ በማርሳቢት አካባቢ ተጨማሪ የመገበያያ ስፍራ ለመክፈት ዝግጅት ማጠናቀቋን አስታወቀች።

በማርሳቢት ግዛት አስተዳደር ጥያቄ እና ድጋፍ የሚቋቋመው የመገበያያ ስፍራ በሽታዎችን እና በአካባቢው ያለውን የኮንትሮባንድ ንግድ ለመቆጣጠር ያችላል ተብሏል።