የሀገር ውስጥ ዜና

በደቡብ ወሎ ዞን ከ350 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ተፈናቃዮች ድጋፍ እየተደረገ ነው

By Feven Bishaw

September 19, 2021

አዲስ አበባ፣ መስከረም 9፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በደቡብ ወሎ ዞን ለሚገኙ ከ350 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ተፈናቃዮች ድጋፍ እያደረኩ ነው አለ የዞኑ አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ጽ/ቤት።

የጽ/ቤቱ ሀላፊ አቶ መሳይ ማሩ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፓሬት እንደተናገሩት ከተለያዩ አካባቢዎች የመጡ ተፈናቃይ የማህበረሰብ ክፍሎችን መንግስት በትኩረት እየደገፈ ነው።